ምርጫ ለይስሙላ (ዶር አክሎግ ቢራራ)

አክሎግ ቢራራ (ዶር)Ethiopian human rights activist Dr. Aklog Birara

በቅርቡ ኢትዮጵያዊያንን ብቻ ሳይሆን የዓለምን ሕዝብ በሚዘገንን ሁኔታ የቀሰቀሰው፤ ያስለቀሰውና ያስቆጣው የኢትዮጵያዊያን ክርስቲያኖች በሊቢያ በሚገኙ የአይሲስ ሽብርተኞች መታረድና በጥይት መርገፍ፤ ወደ አውሮፓ ሲጓዙ በጀልባ መሞት፤ በደቡብ አፍሪካ በሰላም ሲኖሩ በቤንዚን ተቃጥለው መሞት፤ በየመን የርስ በርስ ጦርነት በሳውዶዎች አየር ኃይል ተባራሪ ጥይት መሞት ወዘተ ብቻ አይደለም። በአወንታዊውም፤ የግብፅ መንግሥት ለሞት አደጋ የተዳረጉ ወገኖቻችን ከአደጋ ማትረፉ ሌላው ያልተጠበቀና የሚያበረታታ ዜና ነው። ኢትዮጵያዊያን በያሉበት ጎሳና ኃይማኖት፤ ሃብትና ሞያ፤ ጾታና እድሜ ሳይለዩ በሰብእነታቸውና በኢትዮጵያዊነታቸው ተባብረው ድምጻቸውን ማሰማታቸውም የሚያበረታታ ክስተት ነው። አሁንም ተባብረን ከጩኸት ወደ ድርጊት እንድንራመድ አሳስባለሁ። [ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]

አስተያየት ያስቀምጡ